Telegram Group & Telegram Channel
"ርዕሱን ለአድማጭ"
ርዕሱ ነው
( አምባዬ ጌታነህ )

እኔ የአንቺ ደሐብ-ብኩን ደግ አፍቃሪ፣
ለክብረሽ መግለጫ - ፊደልሽን ቆጣሪ፣
እየተቅለሰለስኩ በልጅሽ ፊት ስኖር፣
ከማዘን በስተቀር ስቄ አላቅም ከምር።
ያም ለዛ ያም ለዛ ሲያጋድል እያየሁ፣
በጊዜ ዳኛ ላይ ፍትህ እየተራብሁ፣
ሁሌ እንዳጉተመተምሁ
'ልጅ አሳድግ ብየ
ካገር እኖር ብየ
ለባሻ ዳርኩለት ሚስቴን 'ህቴ ብየ።'
እንዳለው ገበሬ፣
አለሁኝ እንዳለሁ
ግፍ ሆኖብኝ ክብሬ።

አባት ማጣት ሀዘን - እናት ማጣት ህመም፣
ሆኖ እንደ እግር እሳት እልፍ አመት ቢፈጅም፣
በተበዳይ ልብ ውስጥ ለምፅ እንደሚያሳርፍ ገዳይ አውቆ አያቅም፣
እኔ ያለ ወላጅ መቅረቴ አያመውም።

ሰማይ የግፍ እምባ ሊጥል አቀርዝዟል፣
ጋራ ሸንተረሩ በዝምታ ነግሷል፣
ሜዳ ወንዛ ወንዙ ቅጠሉ ጠንዝሏል፣
እናት ሞቅ አጥልቃ፣
ቁርንጮዋን ታጥቃ፣
ፊቷ ተነጫጭቷል፣
አባት ወደ ማታ ባዘን አጎንብሷል፣
የእኔም የነገ እጣ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ለዛሬ ያለምነው ቅዠት ሲሆን ተስፋ፣
አንተ የፍጥረት አምላክ
የምህረት ዝናብህን ባጥል እንኳ አካፋ።
ነፃ በሆነች ምድር ነፃ አውጪዎች ሞልተው ነፃ ህዝብ ጠፋ።
እኒህ ነፃ አውጪዎች
የለውጡ አምበሳዎች
በቀን አስር ጊዜ ' እመኑን 'የሚሉን፣
ከምናየው እውነት የተፃረረውን
' መሲህ ነን ' የሚሉን
ከእመኑን ባሻገር እንድናምን 'ሚሹት ውሸቱ ምን ይሆን፣

ባለሁለት ወንበር ምቾት ካልተሰማኝ፣
የምለውን ሰምቶ ሰርቶ ካልታዘዘኝ
አባወርነቴን ከተፈታተነኝ
የእሱ መኖር ለእኔ ..
መሄጃ መቆሚያ ማረፊያ ካሳጣኝ፣
እንዴት መላ አላስብ፣
እንዴት ሴራ አልሸርብ
የምን እያቀፉ እንደ ልጅ ማባበል፣
ሳለ ብልህ ዘዴ
በመፈንቅለ ስም መሪነትን መግደል።

እንዲህ ነው እንግዲህ የኛ ዘመን ጣጣ፣
የየዋህ እስትንፋስ የንፁህ እድል እጣ።
ያደለው በሰው ልብ እንደተናፈቀ በክብር ይሞታል፣
ያለደለው ደግሞ የራሱን ቁም ሙቶ ሊገድል ይኖራል፣
ምንድን ነው ሰው መሆን ያዘነ ማስመሰል፣
በውስጥ እየሳቁ ለቅሶ ምን ያደርጋል፣
ፍረድ አንተ ጌታ...
የኃጢያት እልፍኜን
ና ደብድብ ጣራዋን
ወየ ኡኡ ብየ ላቅልጠው ዋይታየን
ቅጣኝ ለክህደቴ
አርገው እውነት የምር የውሸት ለቅሶየን።

እናም በኔ ዘመን...
የእውነት ዘውድ ተጭኖ የሚታየው አሁን፣
ቀዳዳን በር አረጎ ሚያይ ልዩነትን
አንድነትን ትቶ የሚስብክ ጥልን።
በአንድ መንጋ ሚሄድ፣
ያለ ሀሳብ ሚነጉድ
ግን
እስከየት ድረስ ነው?
ጎዳናው ሚያዘልቀው
እስከ መቼ ድረስ በጎጥ አንድ መንገድ፣
በንፁሃን ደም ላይ..
ንፁሃንን ከሶ እያሰሩ መሄድ።
ነውስ?
'ውሻ በቀደደው ጅብ ሠፍቶ ይገባል
ፍየል በግ ቢያጣ እንኳ
ቋንጣውን ሸምጥጦ ይሮጣል እንዲባል
ሆነ በቃ እንግዲህ
የዚች አገር እጣ በተራ መበደል?!

ተው
እንተው
በዳይ ከተበዳይ እኩል ፍትህ ካለ ካልሰከነ ነገር፣
ቤትን ካላቆመ
አንደኛው ጭራሮ ሌላው ሆኖ ማገር፣
ምስጥ የበላት ጎጆ ትመስላለች ሀገር።
"
' ? '
በበረሀ ጋመን ጠውልጎ ያልረባው፣ማውጣት የተሳነው የማህፀንሽ ፍሬ፣
ለአርባ አምስት አመታት ንጉሥ ያልወጣብሽ ምን ኀጥያት ሰርተሽ ነው ንገሪኝ ሀገሬ?

ምንዱባን ኢትዮጵያ - ምትለምኝ ሰጥተሽ፣
ጥበብሽ ሳይቆሽሽ
የምታጥቢ ፈተሽ
ሩህሩኋ የኔ
ጥጥ ፈታይዋ እናቴ፣
ምን ልብ ነው ያለሽ
እኔ እየጠላሁሽ
አንቺ ምትሳሽልኝ ንገሪኝ በሞቴ?

' መደምደሚያ '
በአንድ ቋንቋ ዘየ የሰራነው መንደር፣
ምን ብንኩራራበት አይሆነንም ሀገር።
ይብቃን መጋደሉ፣
ይብቃን መላቀሱ፣
መርገምት ነው ይሄ
እንፀልይ ወደ እርሱ።
ደግሞ
ያሻው ቢከፋኝም፣
ያሻ ብቀየምም፣
ወንድምነትክን ግን
ለሰከንድ አልፍቅም
ሲነኩህ ያመኛል ይሰማዋል ጎኔ፣
ይህ ሁሉ ግፍ ይቁም በአንተ በእሷ በእኔ
ልዩነቱ ይብቃን አንድ እንሁን ወገኔ።


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Getemlemitemaw
@Getem_lemitemaw
@Getemlemitemaw



tg-me.com/Getem_lemitemaw/632
Create:
Last Update:

"ርዕሱን ለአድማጭ"
ርዕሱ ነው
( አምባዬ ጌታነህ )

እኔ የአንቺ ደሐብ-ብኩን ደግ አፍቃሪ፣
ለክብረሽ መግለጫ - ፊደልሽን ቆጣሪ፣
እየተቅለሰለስኩ በልጅሽ ፊት ስኖር፣
ከማዘን በስተቀር ስቄ አላቅም ከምር።
ያም ለዛ ያም ለዛ ሲያጋድል እያየሁ፣
በጊዜ ዳኛ ላይ ፍትህ እየተራብሁ፣
ሁሌ እንዳጉተመተምሁ
'ልጅ አሳድግ ብየ
ካገር እኖር ብየ
ለባሻ ዳርኩለት ሚስቴን 'ህቴ ብየ።'
እንዳለው ገበሬ፣
አለሁኝ እንዳለሁ
ግፍ ሆኖብኝ ክብሬ።

አባት ማጣት ሀዘን - እናት ማጣት ህመም፣
ሆኖ እንደ እግር እሳት እልፍ አመት ቢፈጅም፣
በተበዳይ ልብ ውስጥ ለምፅ እንደሚያሳርፍ ገዳይ አውቆ አያቅም፣
እኔ ያለ ወላጅ መቅረቴ አያመውም።

ሰማይ የግፍ እምባ ሊጥል አቀርዝዟል፣
ጋራ ሸንተረሩ በዝምታ ነግሷል፣
ሜዳ ወንዛ ወንዙ ቅጠሉ ጠንዝሏል፣
እናት ሞቅ አጥልቃ፣
ቁርንጮዋን ታጥቃ፣
ፊቷ ተነጫጭቷል፣
አባት ወደ ማታ ባዘን አጎንብሷል፣
የእኔም የነገ እጣ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ለዛሬ ያለምነው ቅዠት ሲሆን ተስፋ፣
አንተ የፍጥረት አምላክ
የምህረት ዝናብህን ባጥል እንኳ አካፋ።
ነፃ በሆነች ምድር ነፃ አውጪዎች ሞልተው ነፃ ህዝብ ጠፋ።
እኒህ ነፃ አውጪዎች
የለውጡ አምበሳዎች
በቀን አስር ጊዜ ' እመኑን 'የሚሉን፣
ከምናየው እውነት የተፃረረውን
' መሲህ ነን ' የሚሉን
ከእመኑን ባሻገር እንድናምን 'ሚሹት ውሸቱ ምን ይሆን፣

ባለሁለት ወንበር ምቾት ካልተሰማኝ፣
የምለውን ሰምቶ ሰርቶ ካልታዘዘኝ
አባወርነቴን ከተፈታተነኝ
የእሱ መኖር ለእኔ ..
መሄጃ መቆሚያ ማረፊያ ካሳጣኝ፣
እንዴት መላ አላስብ፣
እንዴት ሴራ አልሸርብ
የምን እያቀፉ እንደ ልጅ ማባበል፣
ሳለ ብልህ ዘዴ
በመፈንቅለ ስም መሪነትን መግደል።

እንዲህ ነው እንግዲህ የኛ ዘመን ጣጣ፣
የየዋህ እስትንፋስ የንፁህ እድል እጣ።
ያደለው በሰው ልብ እንደተናፈቀ በክብር ይሞታል፣
ያለደለው ደግሞ የራሱን ቁም ሙቶ ሊገድል ይኖራል፣
ምንድን ነው ሰው መሆን ያዘነ ማስመሰል፣
በውስጥ እየሳቁ ለቅሶ ምን ያደርጋል፣
ፍረድ አንተ ጌታ...
የኃጢያት እልፍኜን
ና ደብድብ ጣራዋን
ወየ ኡኡ ብየ ላቅልጠው ዋይታየን
ቅጣኝ ለክህደቴ
አርገው እውነት የምር የውሸት ለቅሶየን።

እናም በኔ ዘመን...
የእውነት ዘውድ ተጭኖ የሚታየው አሁን፣
ቀዳዳን በር አረጎ ሚያይ ልዩነትን
አንድነትን ትቶ የሚስብክ ጥልን።
በአንድ መንጋ ሚሄድ፣
ያለ ሀሳብ ሚነጉድ
ግን
እስከየት ድረስ ነው?
ጎዳናው ሚያዘልቀው
እስከ መቼ ድረስ በጎጥ አንድ መንገድ፣
በንፁሃን ደም ላይ..
ንፁሃንን ከሶ እያሰሩ መሄድ።
ነውስ?
'ውሻ በቀደደው ጅብ ሠፍቶ ይገባል
ፍየል በግ ቢያጣ እንኳ
ቋንጣውን ሸምጥጦ ይሮጣል እንዲባል
ሆነ በቃ እንግዲህ
የዚች አገር እጣ በተራ መበደል?!

ተው
እንተው
በዳይ ከተበዳይ እኩል ፍትህ ካለ ካልሰከነ ነገር፣
ቤትን ካላቆመ
አንደኛው ጭራሮ ሌላው ሆኖ ማገር፣
ምስጥ የበላት ጎጆ ትመስላለች ሀገር።
"
' ? '
በበረሀ ጋመን ጠውልጎ ያልረባው፣ማውጣት የተሳነው የማህፀንሽ ፍሬ፣
ለአርባ አምስት አመታት ንጉሥ ያልወጣብሽ ምን ኀጥያት ሰርተሽ ነው ንገሪኝ ሀገሬ?

ምንዱባን ኢትዮጵያ - ምትለምኝ ሰጥተሽ፣
ጥበብሽ ሳይቆሽሽ
የምታጥቢ ፈተሽ
ሩህሩኋ የኔ
ጥጥ ፈታይዋ እናቴ፣
ምን ልብ ነው ያለሽ
እኔ እየጠላሁሽ
አንቺ ምትሳሽልኝ ንገሪኝ በሞቴ?

' መደምደሚያ '
በአንድ ቋንቋ ዘየ የሰራነው መንደር፣
ምን ብንኩራራበት አይሆነንም ሀገር።
ይብቃን መጋደሉ፣
ይብቃን መላቀሱ፣
መርገምት ነው ይሄ
እንፀልይ ወደ እርሱ።
ደግሞ
ያሻው ቢከፋኝም፣
ያሻ ብቀየምም፣
ወንድምነትክን ግን
ለሰከንድ አልፍቅም
ሲነኩህ ያመኛል ይሰማዋል ጎኔ፣
ይህ ሁሉ ግፍ ይቁም በአንተ በእሷ በእኔ
ልዩነቱ ይብቃን አንድ እንሁን ወገኔ።


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Getemlemitemaw
@Getem_lemitemaw
@Getemlemitemaw

BY ግጥም ለሚጠማዉ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Getem_lemitemaw/632

View MORE
Open in Telegram


ግጥም ለሚጠማዉ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The lead from Wall Street offers little clarity as the major averages opened lower on Friday and then bounced back and forth across the unchanged line, finally finishing mixed and little changed.The Dow added 33.18 points or 0.10 percent to finish at 34,798.00, while the NASDAQ eased 4.54 points or 0.03 percent to close at 15,047.70 and the S&P 500 rose 6.50 points or 0.15 percent to end at 4,455.48. For the week, the Dow rose 0.6 percent, the NASDAQ added 0.1 percent and the S&P gained 0.5 percent.The lackluster performance on Wall Street came on uncertainty about the outlook for the markets following recent volatility.

Pinterest (PINS) Stock Sinks As Market Gains

Pinterest (PINS) closed at $71.75 in the latest trading session, marking a -0.18% move from the prior day. This change lagged the S&P 500's daily gain of 0.1%. Meanwhile, the Dow gained 0.9%, and the Nasdaq, a tech-heavy index, lost 0.59%. Heading into today, shares of the digital pinboard and shopping tool company had lost 17.41% over the past month, lagging the Computer and Technology sector's loss of 5.38% and the S&P 500's gain of 0.71% in that time. Investors will be hoping for strength from PINS as it approaches its next earnings release. The company is expected to report EPS of $0.07, up 170% from the prior-year quarter. Our most recent consensus estimate is calling for quarterly revenue of $467.87 million, up 72.05% from the year-ago period.

ግጥም ለሚጠማዉ from in


Telegram ግጥም ለሚጠማዉ
FROM USA